መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Thursday, August 19, 2010

መወለድ ቋንቋ ነው።

መወለድ ቋንቋ ነው።

መለያየት ነግሶ ... ብልጥነት አይሎ
መቻቻል ተረስቶ ... ሞኝነት ተብሎ
                    ' ባዳማ ባዳ ነው ' ... ተዘውትሮ በጣም
                    ' ዘመዴ ዘመዴ ' ... ማለት አያዋጣም።
ልብ ተራርቆ ... መግባባት ከታጣ
ዘመድም ባዳ ነው ... መላቅጡን ያጣ
                     ዘር መቁጠር ግን ቀርቶ ... መመቻቸት ቢኖር
                     መወለድ ቋንቋ ነው ... አይደለም ቁምነገር።


18/02/98
አዋሳ

No comments:

Post a Comment