መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Saturday, December 11, 2010

ያማል!

ያማል!

እና እንደነገርኩሽ ...
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
የነፍሰ-ጡርን ሞት አይቶ እንደመሳቀቅ
ባልታሰበ ናዳ ተመትቶ እንደመድቀቅ
ከተስፋ ጉልላት ተገፍቶ እንደመውደቅ
ታምር በበዛባት በዚች ቧልተኛ ዓለም
ከዚህ የበለጠ ምንም ሕመም የለም።
***
አውቶቡሱ ያማል
ሚኒባሱ ያማል
ላዳ ታክሲው ያማል
የማይጎድል የሰው ጎርፍ ... ደራሽ ማዕበሉ
         ... የዕንባ ቅጥልጥሉ
ምን ብዬ ልንገርሽ ... ያማል ይኼ ሁሉ።
***