መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Friday, November 12, 2010

ሌላ ሞክሪ

ሌላ ሞክሪ

ካ'ንጀትሽ ጠልተሽኝ 
       ' አፈር ድሜ  ብላ '
ብለሽ ብትሰድቢኝም
አይሞቅ አይበርደኝም 
አፈርሽ እንደሆን ... አያሳድፈኝም
        ቢሆን ነው ካባዬ
        ድርብርብ ቀሚሴ
        ተጨማሪ ልብሴ

መላ በሉኝ

መላ በሉኝ

ሽፍን ድብቅ ያለ ... እምቅ እጭቅ ያለ
መፍቻ 'ሚሆን ቀመር ... እንደ ስሌት ነገር
ያጣሁለት መላ ... ጥቂት እንዲላላ
************************
ውስብስብ ' ቋጠሮ '
አለመጠን ከ ... ሮ
*************************
ልቤን ልብ ነሳው ... አደብ አቅል አሳጣው
መፈንዳቱ አሰጋኝ ... ልፈታው ቸገረኝ
እንዳሻህ ለማለት ... ትዕግስቱ ባይኖረኝ
**************************
ድሮውንስ ቢሆን የምን ቋጠሮ አለ?
አድናቂ የሌለው በሕሊና ያለ
ስዕል ነው! ... ንድፍ ነው!
ብዬ ላሾፍበት ... አሳር አየሁበት።

Jack Bauar's Final Hour ... What A show!!!