መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Friday, November 12, 2010

መላ በሉኝ

መላ በሉኝ

ሽፍን ድብቅ ያለ ... እምቅ እጭቅ ያለ
መፍቻ 'ሚሆን ቀመር ... እንደ ስሌት ነገር
ያጣሁለት መላ ... ጥቂት እንዲላላ
************************
ውስብስብ ' ቋጠሮ '
አለመጠን ከ ... ሮ
*************************
ልቤን ልብ ነሳው ... አደብ አቅል አሳጣው
መፈንዳቱ አሰጋኝ ... ልፈታው ቸገረኝ
እንዳሻህ ለማለት ... ትዕግስቱ ባይኖረኝ
**************************
ድሮውንስ ቢሆን የምን ቋጠሮ አለ?
አድናቂ የሌለው በሕሊና ያለ
ስዕል ነው! ... ንድፍ ነው!
ብዬ ላሾፍበት ... አሳር አየሁበት።

No comments:

Post a Comment