መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Tuesday, June 29, 2010

የሕሊና ሕግ

የሕሊና ሕግ

የንስሐ አባቴ ልጆቻቸውን ሰብስበው የማስተማር በጎ ልማድ አላቸው ፤ ታዲያ ተሰባስበን በምንማማርበት በአንድ ወቅት ፤ እንወያይበት ዘንድ አንድ ርዕስ አንስተው ነበር " የአንድ ክርስቲያን ሥነ-ምግባር መለኪያው ምንድን ነው? " የሚል ... በወቅቱም ከአንድ ወንድሜ እና ከሦስት እህቶቼ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ብዙ ከተወያየን በኋላ የንስሐ አባታችን የሰጡት ማጠቃለያ በተለይም ሕሊናን የተመለከተው በአእምሮዬ ሲመላለስ የከረመ ነበርና ብዕሬን አነሳሁ።

እኔ እና ወንድሜ

እኔ እና ወንድሜ

የአባቴ እና የአባቱ
የጥንስሳቸው መሰረቱ
ሐረጋቸው ሲመነዘር
አንድ ተብሎ ሲቆጠር
ሀሳባቸውና ፈቃዳቸው
የአኗኗር ቅኝታቸው
ለየቅል የተገነባ
ላይገናኝ ቃል የተጋባ

ነበሩ...አሉ ሁለቱም
የተራራቁ በጣሙን

ወንዘኞችና ጎጠኞች
ለብቻየ የሚሉ ምቀኞች
ልዩነትን እንደ ልዩነት
ያልታደሉ ለመመልከት
ያልነበረውን አንድነት
ያልነበረውን ሕብረት
እንደነበረ የሰበኩ

ነበሩ...ይላሉ የታዘቡ
የትዝብት መጽሐፋቸውን ሲያነቡ