መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Thursday, February 9, 2012

ትንቢተ ዮናስ


ትንቢተ ዮናስ

ምዕራፍ
በሕዝብዋ መካከል ዓመፅ ስለ ጸና
በጣም ተቆጥቼ አዝኛለሁና
ይህን ለነነዌ ንገራት በአዋጅ
አለና ለዮናስ ለአሚታይ ልጅ
እግዚአብሔር አዘዘው እንዲሄድ በቶሎ
ዮናስ እምቢተኛው አሰበ ኮብልሎ
ከአምላክ ተደብቆ አምልጦ ሊጠፋ
ወደ ተርሴስ ሊጓዝ ሄደ ወደ ያፋ
ዋጋ ከፈለና በመርከብ ተሳፍሮ
እያጉረመረመ ባሕሩን ተሻግሮ
ዮናስ ተደብቆ ሲሄድ በግስገሳ
ከእግዚአብሔር ተልኮ ማዕበል ተነሳ
ታላቅ ሞገድ ሆኖ ባሕሩ ተቆጣ
መርከበኞች ፈሩ ትልቅ ሽብር መጣ
መርከቡ እንዲቀልለው እናድርግ እያሉ
አንስተው ብዙ እቃ ወደ ባሕር ጣሉ
ባሕሩም ባሰበት በጣም ተናወጠ
መርከቡ መሰለ የተገለበጠ
ሰው ሁሉ ተነሳ ጸሎት ለማድረስ
ይኽ ሁሉ ሲሆን ተኝቷል ዮናስ
ወደ ዮናስ ሄዶ የመርከቡ አለቃ
ቀሰቀሰውና ከእንቅልፉ ሲነቃ
እግዜር እንዲያድነን ከዚህ ክፉ ጥፋት
ተነስ ጸልይ አለው ይብቃህ ማንቀላፋት
በመርከብ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተሰባስበው
ተመካከሩና በነገሩ አስበው
አለ ኃጢአት ሰርቶ ከእኛ ጋር የመጣ
ለይተን ለማወቅ እንጣጣል ዕጣ
አለዚያ አንድንም ስለተባባሉ
ተሰባሰቡና ዕጣ ቢጣጣሉ
እውነትም እንዳሉት አጥፊው ሰው ታወቀ
በእምቢተኛው ነቢይ በዮናስ ወደቀ
ዮናስ ተረዳና እጁ እንደተያዘ
ያጠፋውን ጥፋት ገልጦ ተናዘዘ
ምነው ባትመጣ ተጣልተህ ከጌታ
እየው መርከባችን እንደሚንገላታ
ቁጣው እንዲታገስ ለማግኘት ጸጥታ
በል አንተው ፍረደን ምን ይበጃል ቢሉ
ዮናስ መለሰና እዚህ ያለ ሁሉ
ስለምን ይጠፋል በኔ የተነሳ
ወደ ባሕር ጣሉኝ አለብኝ አበሳ
ተመልከቱ እነሆ ሥራውን አወቀ
ጥፋቱን ገለጠ ይኸው መች ደበቀ
እሱው ከፈረደ መልሶ በራሱ
ምን እናድርግ ብለው ሊጥሉት ተነሱ
ከደሙ አንጻን ሲሉ ለእግዜር አመልክተው
ወደ ባሕር ጣሉት ዮናስን አውጥተው
በዮናስ ላይ ኖሮ የመጣው ይህ መዓት
ባሕሩ ጸጥ አለ ልክ በዚያው ሰዓት

Tuesday, February 7, 2012

እውን አንተን ወለደ!?


እውን አንተን ወለደ!?

ለተረት ተረትህ ድርጎ መሞገትን ባትወድም

እኔ ከአንተ መልስ እሻለሁ መቸም ላንተ ወሬ አይገድም
አስጠብቦ አያስጨንቅም
ከጀርባ ላብ አያፈልቅም

መልስ ቢጠየፍ ህሊናህ ፌዘኝነትን ወዶ
ከአባትህ የስልጣኔ ሀሁ አቡጊዳህ ተወላግዶ
ከልጅህ ማነን? ጥያቄ ምላሽህ ተካክዶ
ቢሆንም ያለኽው ቅሉ ያባትክን አጽም አስታመህ
ባባትህ ብርሃን ጨልመህ
በስልጣኔው ሰይጥነህ
ቢሆንም ያለኸው ቅሉ
አበው መጠየቅ አይከብድም አሉ
እስቲ ልጠይቅህ ያንተ ማነው አባትህ?

 ያ ስልጣኔንን ቀድሞ የማለደ
በማይነቅዝ ግዙፍ ግብሩ አዲስ ብርሃን የቀደደ
ያ ባየር በረህ የምታየውን ታምር
ባልተጸነሰ ቴክኖሎጅ የማይጠፋ ቅርስ ያኖረ
ያ የላሊበላን መቅደስ ፈልፋይ የአክሱምን ሀውልት ጠራቢ
የጣናን ደብሮች ደባሪ የፋሲልን ግንብ ገንቢ
ያ ስልጣኔን ቀድሞ የማለደ
እውን አንተን ወለደ!?