መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Wednesday, August 11, 2010

ብልጠት ወይስ ሞኝነት?

ብልጠት ወይስ ሞኝነት?

የምኞት ድንበር ሲጣስ
          ራስ
ሁሉን አድራጊ ንጉስ
         ዐይን
አሁንም አሁንም የሚያይ
ሽቅብ ወደላይ ወደላይ።
****************
ሽቅቡን መውጣት መጀመር
     የማይገፋ ነገር
ድንገት ከጫፍ  ቢደረስ
ያሰቡት ከልብ አይደርስ።
****************
ይህን ጊዜ
ትካዜ።
***************
ተመልሶ ለመውረድ
አልቦ መንገድ
መንገዱ ቢኖር
አቅምና መላ ችግር።
**************
እንዲህ ... ውጥንቅጡ የወጣ ጊዜና
'እርሱ ... እግዚአብሔር ነውና
ያሻውን ፤ የፈቀደውን ... ያድርግ ' ማለት
ብልጠት ወይስ ሞኝነት?


22/09/2001
አ.አ

No comments:

Post a Comment