መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Friday, August 6, 2010

" የበላም ለራሱ ...የጾመም ለራሱ " ?

" የበላም ለራሱ ...የጾመም ለራሱ " ?

የበላ ... ለራሱ በላ
* * * * * * *
የበላ ... ሆዱ ሞላ
ሆዱ የሞላ ... ለስጋ ፈቃዱ አደላ
ለስጋ ፈቃዱ ያደላ ... ለነፍሱ ሆነ ተላላ
ለነፍሱ የሆነ ተላላ ... ከፈጣሪው ተጣላ
ከፈጣሪው የተጣላ ... እርሱ በሲኦል እሳት ሊበላ
               ጦሡ ተረፈ ለሌላ።
                 * * * * * * *
የጾመ ... ለራሱ ጾመ
* * * * * * *
የጾመ ... ስጋው ደከመ
በስጋው የደከመ ... የነፍሱን ፈቃድ ፈፀመ
የነፍሱን ፈቃድ የፈፀመ ... በፈጣሪው ፊት ቆመ
በፈጣሪው ፊት የቆመ ... ስለምግባሩ በመልካም ሁሉ ተሾመ
          ስለ'ርሱም ... ሌላው ካገኘው ደዌ ታከመ።

30/11/2002
Tromso, Norway

No comments:

Post a Comment