መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Thursday, August 19, 2010

ዝም ያለ ... ዝም! አለ

ዝም ያለ ... ዝም! አለ

' ዝም
አይነቅዝም ' ሲሉት
... ዝም ሲል
' ዝምታ 
ወርቅ ነው ' ሲሉት 
... ዝም ሲል
' ዝም ባለ አፍ 
ዝምብ አይገባበትም ' ሲሉት
... ዝም ሲል
ዝም! አረጉት አሉ
ወደህ በገባህ እያሉ።

10/01/98
ዲላ

No comments:

Post a Comment