መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Tuesday, August 24, 2010

እናንተን ... " የሴት ልጅ " አሏችሁ?

እናንተን ... " የሴት ልጅ "  አሏችሁ?

' የሴት ልጅ ' ተብላችሁ
በእጅጉ የከፋችሁ
እጃችሁን ... እስቲ ልያችሁ
/ በቃ! ... በቃ! ... በጣም በዛችሁ /
ይኼ መስፈርት ያሻዋል ... ልብ ብላችሁ አድምጡ
ያገባናልም ስትሉ ... ቶሎ ወደ ዳር ውጡ።
*****************************
በመጀመሪያ ...
በኑሮ ትግል ያልተረታ
በውሽንፍሩ ያልተፈታ
የእናቱ ወኔ ያለው 
እርሱ ካለ እንየው
የለም?
******************************
በመቀጠል ...
ማጣት ያላሟጠጠው
' ልጄ ... ልጄ ... ' የሚያስብለው
ፍቅሯ ያለው
እርሱም ካለ እንየው
እርሱም የለም? ...
*******************************
እህ ...
ታዲያ ለምን ከፋችሁ?
እናንተ ' የሴት ልጅ ' አይደላችሁ።

No comments:

Post a Comment