መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Monday, August 16, 2010

መሸ? ፤ ነጋ?

መሸ? ፤ ነጋ?

ልጆቹ ... ልጆቹ
እኒያ ጨቅላዎቹ
ኩኩሉ አኩኩሉ ... እየተባባሉ
ምሽትና ሌቱን ... ቶሎ ያነጋሉ።
ወዲያው ደግሞ ሲያድጉ ... ኩኩን ሲዘነጉ
        ...ጭንቅ ይላቸዋል ...
የቀኑ አመሻሸት ፤ የሌቱ አነጋጉ።


29/10/97
ዲላ

No comments:

Post a Comment