መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Saturday, July 17, 2010

ተረት ተረት

ተረት ተረት

*********
ድ***ሮ***በጥንት ጊዜ ነው አሉ
የዱር አራዊት የተባሉ
በ***ሙ***ሉ
በየወገን በየወገናቸው
በየጫካ በየስርቻቸው
አስተዳዳሪ፤
መሪ፤
የሚሉት ኖሯቸው
ይኖሩ ነበር ደልቷቸው
***ተመችቷቸው።
*************
ከዚያም ሲኖሩ ፣ ሲኖሩ ፣ ሲኖሩ
**************
ከእለታት በአንድ ቀን
አንበሳ የሚሉት ወገን
ከነበረበት ፤ ካለበት ... እምቡር ብሎ ወጥቶ
አራዊቱን ሁሉ በክርኑ እጅ ... አሰጥቶ
ራሱ ሿሚ
እሱው ተሿሚ
ሆኖ አስተዳዳሪ ... የዱር አራዊቱ ሁሉ መሪ
***************
የራሱን የኑሮ ድሎት
የራሱን መንደር ምቹነት
የናንተም ነው እያለ ... እየለፈፈ
ደንቁሮ እያደነቆረ ... ዘመናትን አሳለፈ።
****************
ታዲያ እነርሱም ...
ብ ... ዙ ... በጣም ብዙ ግፍ እየቆጠሩ
ባንበሳው አገዛዝ እየተማረሩ
ብዙ ዘመን ኖሩ።
***************
ጥያቁም ሲያነሱ
... ስለሚደቆሱ
ጨከን ... ጨከን ያሉ
ካያ አንበሳ ይርቃሉ
በሌላ ጫካ ፤ በሌላ ስርቻ
... የስደትን ኑሮ ይገፋሉ።
ለመጨከን ያልታደሉ
በየወገናቸው ያንሾካሹካሉ
ያንሾካሹካሉ ... ያንሾካሹካሉ
ድንገት ጮክ ሲሉ ... ይኮረኮማሉ
ተመልሰው ያንሾካሹካሉ
... ይደቆሳሉ።
ያንሾካሹካሉ ፤ ያንሾካሹካሉ
... ያንሾካሹካሉ ...



02/05/98
አ.አ.

No comments:

Post a Comment