መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Wednesday, July 7, 2010

አንተ 'ወንበር' ... እባክህ ተናገር

አንተ 'ወንበር' ... እባክህ ተናገር

አንተ የኛ ቤት ... ትልቅ 'ወንበር'
እስኪ ተጠየቅ ... በል ተናገር
* * *
አንተን የነካህ ... በ...ሙ...ሉ
ተቀያይሮና ... ተለዋውጦ አመሉ
ጨክን ጨክን ... የሚለዉን
ፍርድ አጓድል ... ያሰኘውን
ንገረን እስኪ ... በሽታውን
* * *
በበፊቱ ወንበር ... መቆርቆር
የኖረው ሁሉ ... ሲያማርር
ቀን ሲወጣ ... እድል ሲያምር
ሲፈናጠጥ ... ያንተን መንበር
የቀየረውን ... በል ተናገር
* * *
ሞገስህ ነው? ድሎትህ?
ሙቀትህ ነው? ቁመትህ?
እባክህ አንተ 'ወንበር'
ጨንቆናልና ተናገር።


12/01/98
ዲላ

No comments:

Post a Comment