መዝሙረ ዳዊት

" እግዚአብሔር አምላኩ የሆነለት ሕዝብ ብፁዕ ነው። " መዝ 32 ፦ 12

Friday, December 2, 2011

በ'ኛ ዘመን

በ'ኛ ዘመን


መቆንጀት ማስጠላት … ማፈርና መኩራት
መሄድ አለመሄድ … ማበድ አለማበድ
መጎበዝ መደደብ … ማሰብ አለማሰብ
መኖር አለመኖር … የትርጉሙ ነገር
             
             ወዳጅነት ፈጥሮ … ጋብቻ መስርቷል።
             ሁሉም ‘ጨዋ’ ሆኖ … የሚያፋታም ጠፍቷል።

እያሰቡ አለማሰብ … እየጎበዙም መደደብ
እየኖሩ አለመኖር … መደንበር መደናገር
            ተወልደዋል።
‘ፍቅር' አሙቀዋል … ‘80' አጽንተዋል።


ማን ያውቃል?
የልጅ ልጃቸውንም … ያሳዩን ይሆናል።
የ‘ሳት ልጅ አመድ ዓይነት … የወላድ መካንም ይሆኑ ይሆናል።
እንዳሻቸው እንደፈለጉም ይሆኑ ይሆናል።
ማን ያውቃል?


ኦላ መገኖ!


ኦላ መገኖ=ጌታ ያውቃል (ጌዴዎኛ)

ግን ግን … በዚህች ቅድስት ሀገር ነውርና ነውረኛ ከጊዜ ወደጊዜ ለመበራከቱ ምህኛት ተብዬው ምን ይሆን?

No comments:

Post a Comment